የሚያዚያ 16፣2016 የዓለም ዜና
ባለፈው ሳምንት በሰነድ ማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አገልጋይ ቀሲስ በላይ መኮንን ዛሬ ለሁለተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡---አዲስ አበባ ዉስጥ የሁለት ቤተሰብ አባላት በሚኖሩበት ቤት ላይ ዛሬ ማለዳ የተናደ ድንጋይና አፈር 7 ሰዎች ገደለ።---ጎርፍ ሰሞኑን ኬንያ ዉስጥ 32፣ ታንዛኒ 58 ሰዎች ሲገድል ቡሩንዲ ዉስጥ ከ100 ሺሕ በላይ ሕዝብ አፈናቅሏል።-----ዓለም ከሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ፍፃሜ ወዲሕ የምትመራበት ሕግና ሥርዓት ከጥፋት አፋፍ ላይ መድረሱን አምንስቲ ኢንተርናሽናል አስታወቀ።