1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ሙዚቃአፍሪቃ

ዝምታ ሰባሪ አዳጊ ሴቶች: የ13 ዓመቷ በገና ደርዳሪ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 19 2015

የ13 ዓመት እድሜ ታዳጊዋ ቢታኒያ ወንድወሰን ነዋሪነነቷ አዲስ አበባ ከተማ ነው፡፡ የ7ኛ ክፍል ተማሪ ስትሆን ቢታኒያ በየአመቱ የክረምት ወራት ላይ የማጠናከሪያ ትምህርት በምትከታተለልበት ወቅት በአጋጣሚ አንድ ሃሳብ መጣላት።

https://p.dw.com/p/4PNcC

ይኼውም በኢትዮጵያ በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የምስጋና ማቅረቢያ መሣሪያ የሆነውን በገና መደርደር መማር፡፡ እንደ ልዩ ቅርስ የሚታየውና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ህልውናው እየተፈታተነ የመጣ የመሰለውን በገና መሟሯ የሚያኮራት ቢታንያ አሁን ላይ የተዋጣላት የበገና ደርዳሪ ለመሆን በቅታለች፡፡ ለመማር የፈጀብኝ ጊዜ ሶስት ወር ነውም ትላለች። #ዝምታሰባሪአዳጊሴቶች #GirlzOffMute
ዘገባ፡ ሱመያ ሳሙኤል
ቪዲዮ፤ ሥዩም ጌቱ